Thursday, September 27, 2012

"ማንም አንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" ማቴ ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፮

ካለፈው  የቀጠለ...   
“ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ ይልቁንም ግለጡት እንጂ” ኤፌ. ፭፥፲፩       
     የተከበራችሁ  አንባብያን“ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ” እና "ማንም አንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" በሚሉት ርዕሶች  የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መሪዎች የቤ/ክ እምነትና ሥርዓቷን ምን እያዛቡ እንደሆነና እንዲሁም እኛ ምዕመናን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የጥፋታቸው ተባባሪ በመሆን ቤ/ክንን ከጸጋ እግዚአብሔር እንድትራቆት ማድረጋችንን በተመለከተ ሰፊ የሆነ ዘገባ ማቅረቤ የሚታወስ  ነው::  ያለንበት ችግር ይህንን ከመሰለ  ከእኛ ምን ይጠበቃል? በሚለው የመፍትሄ ሃሳብ ዙሪያ እንደምንቀጥል ተስፋ በማድረግ በይደር አቆይተነው ነበር:: ይህንንም ችግር እየተመለከተ የሰላም እንቅልፍ የሚተኛ  የተዋህዶ ልጅ ሊኖር ስለማይገባ ምናልባት ያንቀላፋንም ካለን  ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ  “አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሳ ክርስቶስም ያበራልሃል” ኤፌ. 5፥14 ያለውን ቃል ማስታወስ አለብን:: በመሆኑም  መመሪያችን ቃለ  እግዚአብሔር እንደመሆኑ መጠን ከእያንዳንዳችን ምን ይጠበቃል ወደሚለው የማጠቃለያ ሃሳብ ከመሄዳችን በፊት ጸሎትን በተመለከተ ጥቂት ማሳሰብ እፈልጋለሁ::

"ማንም አንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" ማቴ ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፭

ካለፈው  የቀጠለ...
     
     የተከበራችሁ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች ቀደም ሲል“ ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ” ቀጥሎም “ ማንም አንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ”  በሚሉት ርዕሶች ያስነበብናችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነትና ሥርዓቷ ምን ያህል እየተበረዘና እየተከለሰ እንደሆነ ሕዝቡም አሕዛቡም በገሃድ የሚያየውንና የሚሰማውን ችግር ሳይጨምር ቤተክርስቲያንን በሚመሩት በፓትርያርኩ በአባ ጳውሎስ፤ በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ፤ በታላላቅ ሊቃውንትና በቤተ ክህነት ልዩ ልዩ የሃላፊነት ሥራ ላይ በሚገኙ አካላት የተዘጋጁትን ዜና ቤ/ክ ጋዜጣን ፤ የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እምነት፣ ስርዓተ አምልኮትና የውጭ ግንኙነት የሚለውን መጽሐፍ  እንዲሁም የአጣሪ ኮሚሽኑን ሪፖርትና ሌሎችንም ተጨባጭ ማስረጃዎችን መሰረት በማድረግ  የተዘጋጁ ናቸው::

Tuesday, August 14, 2012

"ማንም እንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" ማቴ ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፬

"ማንም እንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" ማቴ ፳፬ ቁ. ፬ ካለፈው  የቀጠለ...
      የተከበራቸሁ አንባብያን ከላይ በተጠቀሰው ርእስ በሶስት ክፍሎች እንዳነበባችሁት በፓትርያርኩ በአባ ጳውሎስ ትእዛዝ በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ስም የተዘጋጀው  የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት፣ ስርዓተ አምልኮትና የውጭ ግንኙነት የተባለው የኑፋቄ መጽሀፍ በነገረ ማርያምና በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት ላይ የሚያስተላልፈውን የተሳሳተ መልእክት ከብዙው በጥቂቱ ማቅረባችን ይታወሳል። በዚህ ጽሁፍ  ደግሞ የምሥጢረ ሥጋዌን ትምህርት የሚያፋልሰውን ክፍል እንመለከታለን::

Sunday, July 15, 2012

“ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ” ማቴ. ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፫


“ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ ማቴ. ፳፬ .  ካለፈው  የቀጠለ::
      የተከበራችሁ አንባብያን  ባለፈው ጽሁፋችን  በፓትርያርኩ አባ ጳውሎስና የሳቸውን አላማ በሚያስፈጽሙ ጳጳሳትና ሊቃውንት የተዘጋጀውየኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ስርዓተ አምልኮትና የውጭ ግንኙነት የተባለው መጽሐፍ ላይ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የጻፉትን የተሳሳተ ትምህርት የመጽሐፉን ገጽ በመጥቀስ ማስነበባችን ይታወሳል:: ከዚህ  በመቀጠል ደግሞ የምሥጢረ ሥላሴን ትምህርት የሚያፋልሰውን  ጽሁፋቸውን እንመለከታለን::

Monday, July 2, 2012

“ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ” ማቴ. ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፪


ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ ማቴ. ፳፬ ቁ. ፬ ካለፈው  የቀጠለ:
         “የኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ትምህርት ትውፊትና ታሪክ ጠብቆ የተዘጋጀ ” የተባለለት መጽሐፍ (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ / እምነት፤ሥርዓተ እምልኮትና የውጭ ግንኙነት) ይ ከሰፈሩት ስህተቶች በጥቂቱ ከዚህ በታች እንመለከታለን::

 1/ በገጽ 37 በምዕራፍ 7 ክብረ ቅድስት ድንግል ማርያም በሚለው ርዕስ ሥር እንዲህ ይላል “ እመቤታችን በዘመኗ ከነበሩት ደናግል ተለይታ እግዚአብሄር ከፈጠራት ጀምሮ  በአሳብ ፤ በመናገር ፤ በመስራት ፤ ንጽሐ ጠባይዕ ያላድፈባት ድንግል ናት::“  በዚህ አረፍተ ነገር ውስጥ ትልቁን ኑፋቄ የያዘው “ በዘመኗ ከነበሩት ደናግል ተለይታ” የሚለው ሐረግ ነው:: ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ለስም አጠራሯ ክብር ምስጋና ይግባትና ምንም እንኳን የሰዎች ትችት ሆነ ስድብ የእመቤታችንን ክብር የሚቀንስ ባይሆንም የነ አባ ጳውሎስ አባባል እመቤታችን ዓለም ሳይፈጠር በአምላክ ልቦና ታስባ የነበረች ፤ ዓለም ከተፈጠረ በኋላ ደግሞ ለአምላክ እናትነት የተመረጠች ንጽህት ቅድስት የዘላለም ድንግል መሆኗን በሚያመለክቱ  ምሳሌዎችና ትንቢቶች በብዙ ነቢያት ሲነገርላት  ቆይቶ ጊዜው ሲደርስ መልእኩ ቅዱስ ገብርኤል አምላካችን እግዚአብሔር ወልድ ሰውን ለማዳን ከእርሷ እንደሚወለድ ባበሰራት ጊዜ  ”እንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ “ ብሎ የሰጠውን ምስክርነት የሚያስተባብል ነው ::

Friday, June 15, 2012

“ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ” ማቴ. ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፩


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ አሜን
“ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ” ክፍል ፩
                                 ማቴ, ፳፬ ቁ, ፬

         በዚህ ጽሑፍ በጥር ወር 1988 ዓ.ም  ”የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እምነት፤ሥርዓተ እምልኮትና የውጭ ግንኙነት ”በሚል ስያሜ የተዘጋጀው መጽሐፍ  ”ሦስት መለኮት“ ከሚለው  ጀምሮ በውስጡ የያዘውን ጎላ ጎላ ያለ ስህተትና ይህንኑ መሰረት በማድረግ የተፈጠሩትን ችግሮች የምንመለከት ሲሆን በቅድሚያ ግን ይህንን የክህደት መጽሐፍ ታዘጋጁት እነማን እንደሆኑ እናያለን::

Friday, June 1, 2012

“ጆሮ ያለው መሰማትን ይስማ” ሉቃስ 8፡8 ክፍል 1



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
የእውነት ምስክርነት 
“ጆሮ ያለው መሰማትን ይስማ” ሉቃስ 8፡8
  
           የክርስትና ሃይማኖት ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ከአባቶች ወደ ልጆች እየተላለፈ ዛሬ እኛ አለንበት ዘመን ደርሷል፡፡ ወደፊትም እስከ ምጽአት ድረስ ይኖራል፡፡ ይህንኑ በማስመልከት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጴጥሮስ “አንተ አለት እንደሆንክ እኔ እነግርሃለሁ በዚያች አለት ላይም ቤተክርስቲያኔን እሰራታለሁ የሲኦል በሮችም አይበረቱባትም” ማቴ 16፡18) በማለት እንደነገረው ቤተክርስቲያን እስከ አለም ፍፃሜ ድረስ በአጋንንትና የነሱ ተገዢ በሆኑ መናፍቃንና ከሃድያን እንደምትፈተን ነገር ግን እንደማይበረቱባት ወይም እንደማያሸንፏት ቃል ገብቶላታል፡፡ እንዲህም ስለሆነ ገና በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ከተነሱት ከቢፅ ሃሳውያን ጀምሮ በዋነኞቹ መናፍቃን በነአርዮስ መቅዶንዮስ ስጥሮስ ልዩንና ሉተር ከነተከታዮቻቸው በከሃድያኑ በነዲዮቅልጥያኖስና መክስምያኖስ በአገራችን በነጉዲትና በነአህመድ ግራኝ ብዙ ተፈትናለች ብዙ ልጆችዋ እምነታችንንና ሥርአታችንን አንለውጥም ብለው ሕይወታቸውን ሰውተዋል በነሱ ሰማእትነት ክርስትና እየተስፋፋ ሄደ እንጂ እንደ ተቃዋሚዎቹ ምኞት ክርስትና ወይንም ቤተክርስቲያን አልጠፋም፡፡
የቀደመው የቤተክርስቲያን ችግር መልክ ነበረው መናፍቃኑ ስለሚያምኑት ነገር በግልጥ ይናገራሉ የቤተክርስቲያን አባቶች በጉባዔ ክርክር ያደርጋሉ መናፍቃኑ ይረታሉ ይወገዛሉ ከሃዲያኑ በበኩላቸው ጣኦት ያቆማሉ ለነሱ የሰገደ ይኖራል አልሰግድም ያለ በሞት ይቀጣል፡፡ የአሁኑ ዘመን ችግር ግን ቤተክርስቲያን ሳይሆኑ ነን በማለት አንዳንድ ሥርዓቶችን ለይምሰል በመፈጸም አመቺ ሁኔታ ሲያገኙ የዋሃን ምእመናንን በተለያ መንገድ እያታለሉ በማስካድ ላይ ናቸው፡፡ ይህ አይነቱ መስሎ የመኖርና የማጭበርበር አካሄድ በተራው ሰው ደረጃ ብቻ ቢደረግ ባላስደነቀም ነበር የሚገርመው ግን የቤተክርስቲያን አባቶች ምእመናንን ከተኩላ ለመጠበቅና ቤተክርስቲያንን ለማስተዳደር ከሰውና ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ከፍተኛ ሃላፊነት በመዘንጋት ተገቢ ያልሆነ ሥራ ሲሰሩ ከማየት የበለጠ አሳዛኝና አሳፋሪ ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡

“ጆሮ ያለው መሰማትን ይስማ” ክፍል 2


3. የኑፋቄ መጽሐፍ አሳትመዋል ለተባለው፡-
1. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክረስቲያን እምነትና ሥርዓት አምኮትና የውጭ ግንኙነት የሚለውን መጽሐፍ ያዘጋጁት 6 ጳጳሳትና 11 በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት ሲሆኑ መጽሐፉ ግን ብዙ ስህተቶችን ይዟል፡፡ ይህን መጽፍ አለቃ ኤሌው ካወገዙትና ምዕመናንም በሰላማዊ ሰልፍ ከተቃወሙት በኋላ ስህተቶቹ ጥቂቶቹ ብቻ በሚስጥር ታርመው ማለት ለምዕመናን ግልጽ ሳይደረግ በድጋሚ የታተመ ተብሎ ተዘግጅቷል፡፡ የመጀመሪያው ጥር 1988 ዓ.ም የታተመ ሲሆን ሁለተኛው በሐምሌ 1988 ዓ.ም ነው፡፡ ችግሩን ለማሳየት ያህል ዋና ዋናዎቹን አምስት ሀሳቦች ከሁለቱም መፃህፍት በቀጥታ ወስደን ስንመለከታቸው ይህንን ይመስላሉ፡፡
ሀ) “እገዚአብሔር ወልድ ሰው በሆነበት ምክንያት “ በሚለው ርዕስ ስር ከገጽ 17 የመጀመሪያው እትም የተወሰደ “ሰው ሆነ ማለት የሰውን ጠባያት፣ ነፍስንና ስጋን በረቂቅ ባህሪው ተዋህደ ማለት ው:: በዚህም የነቢያት ቃል ሁሉ ተፈጸመ” ከገጽ 26 ሁለተኛው እትም የተወሰደ (የታረመው) ‹‹ሰው ሆነ ማለትም በተለየ አካሉ ነፍስንና ሥጋን ተዋሃደ ማለት ነው በዚህም የነቢያት ቃል ሁሉ ተፈፀመ››

“ጆሮ ያለው መሰማትን ይስማ” ሉቃስ 8፡8 ክፍል 3


4. ፓትርያርኩ የሲኖዶስን ሥልጣን የሚሽርና እራሳቸውን በመንፈስ ቅዱስ ቦታ እንዲሰየሙ የሚያደርግ አዲስ ሕግ      አወጡ ለተባለው፤
1. ሚያዚያ 30 ቀን 1988 ዓ.ም ከተዘጋጀው ህገ ቤተ ክርስቲያን
1.1 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 5 የቅዱስ ሲኖዶሱ ሥልጣን ተግባር ተራ ቁ.1 የቅዱስ ሲኖዶሱ በፓትርያርኩ አመራር ሰጪነትና ሰብሳቢነት የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባር ይኖሩታል፡፡
1.2 ምዕራፍ 5 ቀን አንቀፅ 14 የፓትርያርኩ ከማዕረግ መውረድ ተራ ቁ.2 ‹‹ ፓትርያኩ የተዋህዶ ሃይማኖትን የሚያፋልስ ሕግጋት ቤተ ክርስቲያንን የማይብቅ ማዕረጉን የሚያጎድፍ ሆነ መገኘቱ በተጨባጭ ማስተጃ ሲረጋገጥ በምልአተ ጉበዔ ያለ አንዳች የሃሳብ ልዩነት በቅዱስ ሲኖዶስ ከተጠና በኋላ በቅድስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሰረት ከማዕረጉ ይወርዳል፡፡
1.3 ምዕራፍ 8 አንቀጽ 23 የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ፀሀፊ በሚለው ርዕስ ሥር ተራ ቁ. 3/ለ/ ‹‹የሲኖዶሱ ዋና ፀሀፊ የቅዱስ አባልና ፀሀፊ ሆኖ ተጠቲነቱ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ይሆናል፡፡››
1.4 ምዕራፍ 9 አንቀፅ 25…‹‹ከቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት መካከል በቅ/ፓትርያርኩ አቅራቢነት ሶስት ዕጩዎች ተወዳድረው     በቅ/ሲኖዶሱ ምልአተ ጉባኤ የተመረጠው የመንበረ ፓትርያርኩ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ በቅዱስ ፓትርያርኩ ይሾማል፡፡
1.5 ምዕራፍ 16 አንቀፅ 33 ‹‹ካሁን በፊት በቅ/ሲኖዶስ ወጥተው የነበሩ ህጎች በዚህ ሕግ ተሻሽለዋል፡፡
·         የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር አደባባይ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ያለው ችግር እንዲያጣራ ህዳር 5 ቀን 1990 ዓ.ም በፓትርያርኩ ሥልጣን የተሰጠው አጣሪ ኮሚሽን አቅሙ የፈቀደውን ያህል ከላይ የተጠቀሰውን ሕግና ሌሎችንም ችግሮች በማጥናት ሁለት ክፍል ያለው ሪፖርት አቅርቧል፡፡ ከዚህ ውስጥ አዲሱን ህገ ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች ቀድሞ ከነበሩት ህጎች ጋር እንዲህ ያነፃጽረዋል፡፡

Thursday, May 31, 2012

“ጆሮ ያለው መሰማትን ይስማ” ሉቃስ 8፡8 ክፍል 4


5. ጳጳሳትና ኤጴስ ቆጶሳት፣ የቤተክርስቲያን አለቆች፣ ካህናትና ዲያቆናት የወጣውን ህግ መቃወም ሲገባቸው የጥፋቱ ተባባሪ ሆነዋል፣ ፓትርያርኩ እንደ አምላክ ያመልካቸዋል ለተባለው፡-
ሀ) ዜና ቤተክርስትያን ጋዜጣ 50ኛ አመት ቁርር 150 ገጽ 10 ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አለቆች ካህናትና ሰራተኖች ለዘመን መለወጫ የደስታ መገለጫዎች ውስጥ የተወሰደ፡-‹‹እንዚሁም የታሪከዊቷ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ርዕሰ መንበር ሲሆኑ ዘይፈቅድ እምኔክሙ ይኩንክሙ ሊቀ ይኩንክሙ ላዕከ ባለው መሰረት መንፈሳዎ ስራዎችዎ በካኅናትና ምዕመናን ዘንድ ሰርፀው ለምልመውና አብበው ፍሬ እንዲያስገኙ እንደ ትጉህ ገበሬ ያለ እረፍት በየቅዱሳን መካናት እየተዘዋወሩ ቃለ ምዕዳንና ትህትናን የተላበሰ መመሪያ በመስጠት የሚያደርጉት ሃዋርያዊ ጥረትና መንፈሳ የስራ ሂደት አዲስ በመሆኑን ስራው አዲስ ከሆነ ደግሞ የስራው ባለቤት የሆኑት ቅዱስ አባታችን አዲስ ሐዋርያ ነዎትና ‹‹ልብስዎ ለሐዲስ ብእሲ›› ያለውን ቃለ ሐዋርያ መነሻ በማድረግ ውስጣዊ ህሊናችንን ከንዋመ ሀኬት ለስራ የሚቀሰቅሰውን ቅዱስ አባት በስራ፤ በምግባር፣ በሃይማኖት እንከተለው ለማለት ጥቅሱን ለመነሻነት ተጠቅመንበታል፡፡››
ለ) ዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ 50ኛ ዓመት ቁጥር 163 መስከረም 1 ቀን 1990 ዓ.ም ‹‹የአ/አ፤ አድባራት ገዳማት እራሱን ‹‹መርሀ ተወህዶ›› ብሎ የሚጠራውን ፀረ ቤተ ክርስቲያን ቡድን አውገዙ›› በሚለው ርዕስ ስር የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪዎች ፣ የሰበካ ጉባኤ አባላት የሰንበት ት/ቤት አባላት ፤ የየአጥቢያ ቤ/ክ ሰራተኞች በተገኙበት ስብሰባ ላይ የቀረበ ፅሁፍ ነው፡- ገፅ 10 እና 13