Thursday, July 25, 2013

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል ሶስት

ካለፈው የቀጠለ
       የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች፣

ን ዝም አልልም ” በሚለው ርዕስ ባለፉት ሁለት ተከታታይ ክፍሎች በቅድስት ቤ/ክ ውስጥና በዙሪያዋ የሚከናወነው ንግድ የተወገዘ እንደሆነ የጌታችንን ወንጌል ጠቅሰን ባቀረብነው ጽሁፍ ጥሩ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ ተስፋ በማድረግ በሶስተኛው ክፍል ደግሞ የዘመናችን የቤ/ክ መሪዎችም ቅድስት ቤ/ክ ከተልእኮዋ ውጪ  በዚሁ የንግድ ስራ እንድትሰማራ ያደረጉበትን ሁኔታ እንመለከታለን::

ሐ/ በቅድስት ቤ/ክ የተቋቋሙ የንግድ ማዕከላት

        ሁላችንም እንደምናውቀውና እንደምናየው በአሁኑ ጊዜ እንኳን ረጅም እድሜና ሰፋፊ ቦታ ያላቸው ይቅሩና በቅርብ ጊዜያት የተተከሉት አብያተ ክርስቲያናት ሳይቀሩ ገና በመቃረቢያ/ መቃኞ/ እያሉ ማለትም ዋናው ቤ/ክ ሳይጀመር በቅድሚያ የሚሰራው የንግድ ቤት ነው::አንጋፋዎቹና ሰፋ ያለ ቦታና የገንዘብ አቅሙ ያላቸው አብያተ ክርስቲያናት ደግሞ ትላልቅ ፎቆችን እየገነቡ የንግድ ስራውን በሰፊው ሲያከናውኑት ይታያል:: ሁኔታውን በማስተዋል ከተመለከትነው አባቶቻችን ባወረሱን  መሰረት ከዋናው ህንፃ ቤ/ክ በተጨማሪ የሚሰሩት ለቤ/ክ አገልግሎት የሚሰጥባቸው ቢሮዎች ማለትም የሰበካ ጉባኤ ፣ የስብከተ ወንጌል፣የካህናት አስተዳደር፣ የሰ/ት/ቤት አዳራሽና  እንዲሁም የጽዋ ማህበራትና የሰንበቴ ቤትን የመሳሰሉትን  እንጂ የንግድ ቤቶችን ሰርተው አላስረከቡንም።

Monday, April 15, 2013

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል ሁለት

ካለፈው የቀጠለ
     የተከበራችሁ የቅድስት  ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች
     ባለፈው ስለ ጽዮን ዝም አልልም በሚለው ርዕስ ሥር የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርት " በሚለው ንዑስ  ርዕስ በቤ/ልንፈጽማቸው ከማይገቡ ተግባራት አንዱ የሆነውን የንግድ ሥራ በቅጥረ / እንዳንፈጽም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስያስተማረንንና ወንጌላውያንም የጻፉልንን በጥቂቱ ተመልክተን በይደር አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል::ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ይህንንየጌታችንን ቃል በድፍረት ተራምደው ቅድስት /ክንን የንግድ ማዕከል ያደረጉዋትን ክፍሎች በሦስት ከፍለን የምንመለከታቸው ሲሆንከሁሉ አስቀድመን ልንገነዘበው የሚገባን የንግዱ ተዋናዮች ማለትም ሻጮችም ሆኑ ገዢዎቹ የዚችው የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆችመሆናቸውን ነው፡፡
     የዚህ ርዕስ ዓላማ በቤ/ ምንም ዓይነት የንግድ ሥራ መከናወን እንደሌለበት ማስገንዘብ ስለሆነ ነጋዴዎች ለሕብረተሰቡየሚያቀርቡትን የሸቀጥ ዝርዝር ማቅረብ አስፈላጊ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ቁጥሩ ከመብዛቱ የተነሳ ጸሐፊውንም ሆነ አንባቢውንከማሰልቸት በቀር ሌላ ጥቅም የለውም፡፡ሆኖም ለችግሩ አጽንኦት እንዲሰጠውና ወደ መፍትሔውም ለመሄድ አንዲቻል በጥቂቱ መጥቀሱግድ ነው፡፡ ነጋዴዎች መደበኛ ሥራቸው ንግድ ስለሆነ ምዕመናኑ ለዕለት ከዕለት ኑሮው የሚፈልጋቸውን ሸቀጦች ለይተው ያውቃሉ፡፡እነዚህም ከእርጥብ በሶቢላ ጀምሮ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች፣ አዳዲስና ያገለገሉ ልብሶችና ጫማዎች፣የውበት ዕቃዎች፣ የቤትዕቃዎች፣የተለያዩ ሎተሪዎች እንዲሁም ለባዕድ አምልኮ አገልግሎት የሚውሉ የጢሳ ጢስ ዓይነቶችን ሳይቀሩ በስፋት ተዘርግተው ሲሸጡይታያል፡፡

Sunday, January 13, 2013

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል አንድ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
“የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ ፤አንባቢው ያስተውል…”ማቴ.24፥15

    የተከበራችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆች፦ እንደምን ሰንብታችኋል? በቸርነቱና በቅዱሳኑ ቃል ኪዳን እየጠበቀ እዚህ ያደረሰን ፈጣያችን ልዑል እግዚአብሔር ስሙ  እስከ ዘለዓለም ድረስ የተመሰገነ ይሁን፡፡ “ጆሮ ያለው መስማትን ይስማ ” እና “ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ ” በሚት ርዕሶች በቤ/ክ ስም የተዘጋጁ ነገር ግን የቤ/ክንን እምነትና ሥርዓት እንዲሁም ትውፊቷን ሳይቀር የሚያፋሱትን መጻሕፍት በመጥቀስ የተዘጋጀውን ሰፊ ዘገባ እንደተመለከትን ሁሉ በዚህም ርዕስ ደግሞ በቅድስት ቤ/ክ ሊደረጉ የማይገባቸው ነገር ግን በስፋት እየተፈጸሙ ያሉትን ­­­­­­­­­­­ጥፋቶች እንመለከታለን፡፡የዚህም ጽሑፍ አዘጋጅ ዋና ዓላማ ሁላችን የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆች ወደ ማስተዋል ተመልሰን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ከምንሰራው ስህተት እንድንመለስ ለማሳሰብ ነው፡፡   
   ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰማይንና ምድርን ለማሳለፍ የሚመጣበት ጊዜ ሲቃረብ የሚታዩትን ምልክቶች ለቅዱሳን ሐዋርያት በዝርዝር የነገራቸውን በወንጌል ስናነብ (በማቴ.24፥1-ፍጻሜ፤ ማር.13፥1-ፍጻሜ፤ ሉቃ.21፥5-36 ) እኛ ያለንበት ዘመን ትንቢቶቹ በብዛት እየተፈጸሙ እንደሆነ ያመለክተናል፡፡ከነዚህም የዓለም ፍጻሜ የመቃረቡ ምልክቶች አንዱ “የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ ፤አንባቢው ያስተውል…ማቴ.24፥15 በማለት ጌታችን መድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረው ትንቢት ነው፡፡ጌታችንም ይህንን ትምህርት ያስተማረው አስቀድሞ ነቢዩ ዳንኤል  የተናገረውን  በመጥቀስ ሲሆን ትንቢቱም እንዲህ የሚል ነው፡፡ “ከእርሱም ጋር ሠራዊቶች ይቆማሉ ፤መቅደሱንም ግንቡንም ያረክሳሉ፤ የዘወትሩንም መሥዋዕት ያስቀራሉ፤ የጥፋትንም ርኩሰት ያቆማሉ፡፡” ዳን.11፥31 ፡፡ ይህ የርኩሰት ሥራ በኢአማንያኑ ብቻ የሚፈጸም ቢሆን ባላሰደነቀም ነበር፡፡የበለጠ የሚያሳዝነው ግን ቤ/ክ እናከብራለን የምንለው ሰዎች የእግዚአብሔርን ማደሪያ ቅድስት ቤ/ክንን በተለያየ ነገር እያረከስናት መሆኑ ነው፡፡ከነዚህም ጥፋቶች ውስጥ በቅድሚያ አንዱን ብቻ እንመለከታለን፡፡