በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ
ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
"ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ
መገዛት አትችሉም" ሉቃስ 16፤13
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች!
እንደምን ሰነበታችሁ?
“ስለጽዮን ዝም አልልም ” በሚለው ርዕስ ባለፉት ሦስት ተከታታይ ክፍሎች በቅድስት ቤ/ክ ውስጥና በዙሪያዋ በማንኛውም ሁኔታ የሚከናወነው ንግድ የተወገዘ እንደሆነ የጌታችንን ወንጌል መሰረት አድርገን ብዙ ተማምረናል፡፡እንዲሁም በክፍል አራትና አምስት ደግሞ
ይኸው አላስፈላጊ የቤተ ክርስቲያን የንግድ ሥራ እያስከተለ ያለውን ችግር በማስመልከት ‹‹ሐራ ዘተዋህዶ›› ከተባለው ድረ ገጽ ያገኘነውን ጽሁፍ ተመልክታችሁ ስለ ችግሩ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ
ተስፋ እናደርጋለን፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ "ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም" በሚል
ርዕስ እንማማራለን፡፡
መልካም ንባብ!