Sunday, March 6, 2016

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል ስድስት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

"ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም" ሉቃስ 16፤13
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች!
እንደምን ሰነበታችሁ?
ን ዝም አልልም ” በሚለው ርዕስ ባለፉት ሦስት ተከታታይ ክፍሎች በቅድስት ቤ/ክ ውስጥና በዙሪያዋ በማንኛውም ሁኔታ የሚከናወነው ንግድ የተወገዘ እንደሆነ የጌታችንን ወንጌል መሰረት አድርገን ብዙ ተማምረናል፡፡እንዲሁም በክፍል አራትና አምስት ደግሞ ይኸው አላስፈላጊ የቤተ ክርስቲያን የንግድ ሥራ እያስከተለ ያለውን ችግር በማስመልከት ‹‹ሐራ ዘተዋህዶ›› ከተባለው ድረ ገጽ ያገኘነውን ጽሁፍ ተመልክታችሁ ስለ ችግሩ መጠነኛ ግንዛቤ እንዳገኛችሁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ "ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ መገዛት አትችሉም" በሚል ርዕስ እንማማራለን፡፡ 
መልካም ንባብ!

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል አምስት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
       
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች፣
“ስን ዝም አልልም ” በሚለው ርዕስ በክፍል አራት‹‹ሐራ ዘተዋሕዶ›› ከተሰኘው ድረ ገጽ ላይ ያገኘነውን ጽሁፍ ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበንላችሁ እንደነበር ይታወሳል፡፡አሁንም የዚያኑ ጽሁፍ ተከታዩን ክፍል እድታነቡ እየጋበዝን፤የዚህ ጽሁፍ ዋና ዓላማ ፤ይህንን የቤተ ክርስቲያን ችግር አውቀን፤ ከእኛ ምን ይጠበቃል? ብለን ወደ መፍትሄ የሚያደርሰንን መንገድ እንድንቀይስ እንጂ ችግሩን ብቻ እያወራን እንድንኖር አይደለም፡፡ስለሆነም ጉዳዩ ይመለከተኛል የምንል ሁላችን የእናታችን የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዶግማዋ፣ሥርዓቷና ትውፊቷ እንዲሁም ሀብትና ንብረቷ በአግባቡ ተጠብቆ ከአባቶቻችን በተረከብንበት ሁኔታ፤ እኛም ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ አለብን፡፡ስለዚህ ማንኛውም መንፈሳዊ ሥራ በእኛ ጥረት ብቻ ውጤታማ ሊሆን ስለማይችል፤በጾምና  በጸሎት ፈቃደ እግዚአብሔርን ከመማጸን ጋር አቅማችን የሚፈቅደውን ሁሉ ለማድረግ የምንነሳበት ጊዜው አሁን መሆኑን ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን የመናፍቃን፤የሌቦችና የወንበዴዎቸ ዋሻ ከመሆን ይጠብቅልን፡፡
መልካም ንባብ!