Monday, April 15, 2013

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል ሁለት

ካለፈው የቀጠለ
     የተከበራችሁ የቅድስት  ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች
     ባለፈው ስለ ጽዮን ዝም አልልም በሚለው ርዕስ ሥር የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርት " በሚለው ንዑስ  ርዕስ በቤ/ልንፈጽማቸው ከማይገቡ ተግባራት አንዱ የሆነውን የንግድ ሥራ በቅጥረ / እንዳንፈጽም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስያስተማረንንና ወንጌላውያንም የጻፉልንን በጥቂቱ ተመልክተን በይደር አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል::ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ይህንንየጌታችንን ቃል በድፍረት ተራምደው ቅድስት /ክንን የንግድ ማዕከል ያደረጉዋትን ክፍሎች በሦስት ከፍለን የምንመለከታቸው ሲሆንከሁሉ አስቀድመን ልንገነዘበው የሚገባን የንግዱ ተዋናዮች ማለትም ሻጮችም ሆኑ ገዢዎቹ የዚችው የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆችመሆናቸውን ነው፡፡
     የዚህ ርዕስ ዓላማ በቤ/ ምንም ዓይነት የንግድ ሥራ መከናወን እንደሌለበት ማስገንዘብ ስለሆነ ነጋዴዎች ለሕብረተሰቡየሚያቀርቡትን የሸቀጥ ዝርዝር ማቅረብ አስፈላጊ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ቁጥሩ ከመብዛቱ የተነሳ ጸሐፊውንም ሆነ አንባቢውንከማሰልቸት በቀር ሌላ ጥቅም የለውም፡፡ሆኖም ለችግሩ አጽንኦት እንዲሰጠውና ወደ መፍትሔውም ለመሄድ አንዲቻል በጥቂቱ መጥቀሱግድ ነው፡፡ ነጋዴዎች መደበኛ ሥራቸው ንግድ ስለሆነ ምዕመናኑ ለዕለት ከዕለት ኑሮው የሚፈልጋቸውን ሸቀጦች ለይተው ያውቃሉ፡፡እነዚህም ከእርጥብ በሶቢላ ጀምሮ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች፣ አዳዲስና ያገለገሉ ልብሶችና ጫማዎች፣የውበት ዕቃዎች፣ የቤትዕቃዎች፣የተለያዩ ሎተሪዎች እንዲሁም ለባዕድ አምልኮ አገልግሎት የሚውሉ የጢሳ ጢስ ዓይነቶችን ሳይቀሩ በስፋት ተዘርግተው ሲሸጡይታያል፡፡