4. ፓትርያርኩ የሲኖዶስን ሥልጣን የሚሽርና እራሳቸውን በመንፈስ ቅዱስ ቦታ እንዲሰየሙ የሚያደርግ አዲስ ሕግ አወጡ ለተባለው፤
1. ሚያዚያ 30 ቀን 1988 ዓ.ም ከተዘጋጀው ህገ ቤተ ክርስቲያን
1.1 ምዕራፍ 3 አንቀፅ 5 የቅዱስ ሲኖዶሱ ሥልጣን ተግባር ተራ ቁ.1 የቅዱስ ሲኖዶሱ በፓትርያርኩ አመራር ሰጪነትና ሰብሳቢነት የሚከተሉት ሥልጣንና ተግባር ይኖሩታል፡፡
1.2 ምዕራፍ 5 ቀን አንቀፅ 14 የፓትርያርኩ ከማዕረግ መውረድ ተራ ቁ.2 ‹‹ ፓትርያርኩ የተዋህዶ ሃይማኖትን የሚያፋልስ ሕግጋት ቤተ ክርስቲያንን የማይጠብቅ ማዕረጉን የሚያጎድፍ ሆነ መገኘቱ በተጨባጭ ማስተጃ ሲረጋገጥ በምልአተ ጉበዔ ያለ አንዳች የሃሳብ ልዩነት በቅዱስ ሲኖዶስ ከተጠና በኋላ በቅድስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሰረት ከማዕረጉ ይወርዳል፡፡
1.3 ምዕራፍ 8 አንቀጽ 23 የቅ/ሲኖዶሱ ዋና ፀሀፊ በሚለው ርዕስ ሥር ተራ ቁ. 3/ለ/ ‹‹የሲኖዶሱ ዋና ፀሀፊ የቅዱስ አባልና ፀሀፊ ሆኖ ተጠቲነቱ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ይሆናል፡፡››
1.4 ምዕራፍ 9 አንቀፅ 25…‹‹ከቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት መካከል በቅ/ፓትርያርኩ አቅራቢነት ሶስት ዕጩዎች ተወዳድረው በቅ/ሲኖዶሱ ምልአተ ጉባኤ የተመረጠው የመንበረ ፓትርያርኩ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆኖ በቅዱስ ፓትርያርኩ ይሾማል፡፡
1.5 ምዕራፍ 16 አንቀፅ 33 ‹‹ካሁን በፊት በቅ/ሲኖዶስ ወጥተው የነበሩ ህጎች በዚህ ሕግ ተሻሽለዋል፡፡
· የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር አደባባይ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ያለው ችግር እንዲያጣራ ህዳር 5 ቀን 1990 ዓ.ም በፓትርያርኩ ሥልጣን የተሰጠው አጣሪ ኮሚሽን አቅሙ የፈቀደውን ያህል ከላይ የተጠቀሰውን ሕግና ሌሎችንም ችግሮች በማጥናት ሁለት ክፍል ያለው ሪፖርት አቅርቧል፡፡ ከዚህ ውስጥ አዲሱን ህገ ቤተ ክርስቲያን ከሌሎች ቀድሞ ከነበሩት ህጎች ጋር እንዲህ ያነፃጽረዋል፡፡