Tuesday, August 14, 2012

"ማንም እንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" ማቴ ፳፬ ቁ. ፬ ክፍል ፬

"ማንም እንዳያስታቸሁ ተጠንቀቁ" ማቴ ፳፬ ቁ. ፬ ካለፈው  የቀጠለ...
      የተከበራቸሁ አንባብያን ከላይ በተጠቀሰው ርእስ በሶስት ክፍሎች እንዳነበባችሁት በፓትርያርኩ በአባ ጳውሎስ ትእዛዝ በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ስም የተዘጋጀው  የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት፣ ስርዓተ አምልኮትና የውጭ ግንኙነት የተባለው የኑፋቄ መጽሀፍ በነገረ ማርያምና በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት ላይ የሚያስተላልፈውን የተሳሳተ መልእክት ከብዙው በጥቂቱ ማቅረባችን ይታወሳል። በዚህ ጽሁፍ  ደግሞ የምሥጢረ ሥጋዌን ትምህርት የሚያፋልሰውን ክፍል እንመለከታለን::