Monday, April 15, 2013

ስለ ጽዮን ዝም አልልም!!! ኢሳ.62፥1 ክፍል ሁለት

ካለፈው የቀጠለ
     የተከበራችሁ የቅድስት  ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች
     ባለፈው ስለ ጽዮን ዝም አልልም በሚለው ርዕስ ሥር የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርት " በሚለው ንዑስ  ርዕስ በቤ/ልንፈጽማቸው ከማይገቡ ተግባራት አንዱ የሆነውን የንግድ ሥራ በቅጥረ / እንዳንፈጽም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስያስተማረንንና ወንጌላውያንም የጻፉልንን በጥቂቱ ተመልክተን በይደር አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል::ከዚህ በመቀጠል ደግሞ ይህንንየጌታችንን ቃል በድፍረት ተራምደው ቅድስት /ክንን የንግድ ማዕከል ያደረጉዋትን ክፍሎች በሦስት ከፍለን የምንመለከታቸው ሲሆንከሁሉ አስቀድመን ልንገነዘበው የሚገባን የንግዱ ተዋናዮች ማለትም ሻጮችም ሆኑ ገዢዎቹ የዚችው የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ልጆችመሆናቸውን ነው፡፡
     የዚህ ርዕስ ዓላማ በቤ/ ምንም ዓይነት የንግድ ሥራ መከናወን እንደሌለበት ማስገንዘብ ስለሆነ ነጋዴዎች ለሕብረተሰቡየሚያቀርቡትን የሸቀጥ ዝርዝር ማቅረብ አስፈላጊ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን ቁጥሩ ከመብዛቱ የተነሳ ጸሐፊውንም ሆነ አንባቢውንከማሰልቸት በቀር ሌላ ጥቅም የለውም፡፡ሆኖም ለችግሩ አጽንኦት እንዲሰጠውና ወደ መፍትሔውም ለመሄድ አንዲቻል በጥቂቱ መጥቀሱግድ ነው፡፡ ነጋዴዎች መደበኛ ሥራቸው ንግድ ስለሆነ ምዕመናኑ ለዕለት ከዕለት ኑሮው የሚፈልጋቸውን ሸቀጦች ለይተው ያውቃሉ፡፡እነዚህም ከእርጥብ በሶቢላ ጀምሮ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች፣ አዳዲስና ያገለገሉ ልብሶችና ጫማዎች፣የውበት ዕቃዎች፣ የቤትዕቃዎች፣የተለያዩ ሎተሪዎች እንዲሁም ለባዕድ አምልኮ አገልግሎት የሚውሉ የጢሳ ጢስ ዓይነቶችን ሳይቀሩ በስፋት ተዘርግተው ሲሸጡይታያል፡፡
     ነጋዴዎቹ ይህንን የተቀደሰ የጸሎት ሥፍራ መሸጫና መለወጫ ያደረጉበት ምክንያት ምንድነው ምዕመናንስ  በቅድስት /የሚሸጡትን ሸቀጦች ለምን ይገዛሉ ብለን ብንጠይቅ የምናገኘው መልስ ከብዙ በጥቂቱ ይህንን ይመስላል᎓᎓

በልዩ ልዩ የንግድ ዓይነቶች የተሰማሩ ነጋዴዎች

1/ 
በበዓላት ቀኖች ብዙ ምዕመናን ወደ / ስለሚሄዱና ብዙ ገዢ ስለሚያገኙ 
2/
ብዙዎቹ መደበኛ የሆነ ሱቅ ስለሌላቸውና  ያላቸውም ቢሆኑ ብዙ የንግድ ልውውጥ ስለማያገኙ፣
3/ 
አንዳንዶቹም ይህ ድርጊታቸው አግባብ አለመሆኑን  ስለማያውቁ፣
4/ 
በየደረጃው የሚገኙ የቤ/ አስተዳዳሪዎችአገልጋዮችበማወቅም ይሁን ባለማወቅ /ክንን የንግድ ቤት ያደረጉትን ነጋዴዎችበመከልከል ህገ / እንዲከበር ባለማድረጋቸው ሲሆን ሌሎችም ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ᎓᎓
ይህንን ህግ መተላለፍ የሚያስከትለው ችግር
ዕቃዎቻቸውን ለማስዋወቅ በሚፈጥሩት ጫጫታና ሁካታ ለጸሎት በተሰበሰቡት ምዕመናን ላይ ከፍተኛ    ተጽዕኖ ያሳድራል፡፡
ቅድስት /ክንን ለመናፍቃንና ለአሕዛብ መሳለቂያ እንድትሆን ያደርጋታል፡፡
ትዕዛዘ እግዚአብሔርን በመጣሳቸው ክፉ ሥራቸውን አቁመው ንስሃ ካልገቡ በኃጢአቱ
 
ይጠየቁበታል፡᎓
የቤ/ አስተዳዳሪዎችምአገልጋዮችም/  ጥፋቱን እያዩ በቸልተኝነት በማለፋቸው ከልዑል እግዚአብሔር ፍርድ
 አያመልጡም᎓᎓

ዕቃውን የሚገዙ ምዕመናን

1/ በአንድ ወንጭፍ ሁለት ወፍእንደሚባለው ከቤ/ ተመልሶ ወደ ተለያዩ ሱቆች ከመሄድ  የነፍስንም የሥጋንም ገበያ በአንድ ላይአከናውኖ በመመለስ ጊዜንና ጉልበትን ገንዘብንም ጭምር ለመቆጠብ የሚደረግ የብልጠት ሥራ፣
2/ በዚህ የሚሸጡት ዕቃዎች በመደበኛ ሱቆች ከሚሸጡበት መጠነኛ የዋጋ ቅናሽ ስላላቸው፣
3/ 
የነጋዴዎቹ ከፍተኛ የሆነ የማግባባት ችሎታ የገዥውን ትኩረት የሚስብ በመሆኑ፣
4/ 
ነጋዴዎቹ የሚያቀርቡዋቸው ዕቃዎች ሌላ ቦታ በቀላሉ የማይገኙ መሆናቸውና ሌሎችም ናቸው᎓᎓
ይህንን ህግ መተላለፍ የሚያስከትለው ችግር
ከቅድስት /ክን ልናገኝ የምንሻውን በረከት የምንቀበው ልማዳችንን ለማድረስ በምናደርገው ምልልስ ሳይሆን ህገ እግዚአብሔርንናሥርዓተ /ክን አክብረን በምንፈጽመው አገልግሎት ብቻ ስለሆነ በዚህ በተሳሳተ መንገድ የሚጓዙ ሁሉ በረከት አልባ ሆነው ይመለሳሉ፡፡
ከላይ እንደተገለጸው “የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጓት"  የሚለው ጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትዕዛዝ ሻጮችን ብቻ ሳይሆንገዢዎችንም የሚመለከት በመሆኑ ይህንን ቃል ተላልፎ በቅድስት /ክን ቅጥር የሚሸጡትን ሸቀጣ ሸቀጦች መግዛት ንስሃ ካልገቡበስተቀር ኃጢአት ነውና ያስኮንናል፡፡
     ከላይ አጠር አድርገን እንዳየነው በቤ/ ውስጥና በዙሪያዋ የሚከናወነው የሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ አግባብ አለመሆኑን ሁሉም ክፍልከተስማማበትና እናስተካክለው ካልንም በቀላሉ መፍትሄ ልንሰጠው የምንችለው ነገር ነው᎓᎓ይኸውም በምዕመናን በኩል በቤ/ አካባቢምንም ዓይነት ግብይት አለማድረግ ሲሆን ነጋዴዎቹን ደግሞ በቤ/ አካባቢመገበያየት ኃጢአት መሆኑን ከማስረዳት ጋር እንዳይነግዱመከልከል ብቻ ነው᎓᎓

በቅድስት / የንግድ ማዕከላት

     በጣም የሚያሳዝነውና ሥር ከመስደዱ የተነሳ ለማስተካከልም ብዙ ሥራ የሚጠይቀው ጥፋት  በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥበልማትና በመንፈሳዊ አገልግሎት ሥም የገባው ንግድ ሲሆን ይህንንም በየመልኩ እንመለከተዋለን᎓᎓እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በሌላ ጊዜእንገናኛለን ᎓᎓ ለዛሬው ይቆየን᎓᎓

No comments:

Post a Comment