Friday, August 23, 2019

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሰላሳ ሁለት


ከክፍል ሰላሳ አንድ የቀጠለ
     የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
     ከዚህ በመቀጠል ከ"ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ" ፌስ ቡክ ገጽ ያገኘነውን እጅግ ጠቃሚ ትምህርት አቅርበንላችኋል፡፡ በጽሑፉ ላይ አልጨመርንም አልቀነስንም፡፡

መልካም ንባብ!

Sunday, September 16, 2018

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሰላሳ አንድ


ከክፍል ሰላሳ የቀጠለ
የዶግማና የቀኖና ጥሰት በኢ/ኦ/ ተ/ ቤተ ክርስቲያን፤ ክፍል ሰባት
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?
ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
      በጥር ወር 1988 ዓ.ም ለሽያጭ የቀረበውና "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ እምነት፤ሥርዓተ ምልኮትና የውጭ ግንኙነት " በሚል ስያሜ የተዘጋጀው የኑፋቄ መጽሐፍ ያዘጋጁትና የእርማት ሥራውን የሰሩት እነማን እንደሆኑ እንድረዱ በማሰብ ከመጽሐፉ ውስጥ ባገኘነው መሠረት እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡

Tuesday, August 21, 2018

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሰላሳ

ከክፍል ሃያ ዘጠኝ የቀጠለ
የዶግማና የቀኖና ጥሰት በኢ/ኦ/ ተ/ ቤተ ክርስቲያን፤ ክፍል ስድስት
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?
ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       ባለፉው ክፍል 29 ጸሁፋችን ታላቁ ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ ያስተላለፉትን ውግዘትና ማስረጃዎቹን፤እንዲሁም ውግዘቱን ላለመቀበል የሚቀርቡ ምክንያቶችን  አስነብበናችሁ ቀጣዩን ክፍል "ከእኛ ምን ይጠበቃል" በሚለው ሃሳብ እንመለሳለን ብለን እንደነበር ይታወሳል፡፡ይህ የቤት ሥራችን እንደተጠበቀ ሆኖ ለዛሬው ከአባታችን ከአለቃ አያሌው በስማቸው ከተከፈተው ድረ-ገጽ www.aleqayalewtamiru.info ላይ ያገኘነውን ለአስራ አንደኛ ዓመት መታሰቢያቸው የቀረበውን ጽሁፍ ሳንጨምርና ሳንቀንስ አቅርበንላችኋል፡፡
ሰምተን ለመጠቀም ያብቃን፡፡

Monday, August 20, 2018

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሃያ ዘጠኝ

 ከክፍል ሃያ ስምንት የቀጠለ
የዶግማና የቀኖና ጥሰት በኢ/ኦ/ ተ/ ቤተ ክርስቲያን፤ ክፍል አምስት
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?
ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       ባለፉው ክፍል 28 ጸሁፋችን ታላቁ ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ ያስተላለፉትን ውግዘት አስነብበናችሁ፤በቀጣይ ስለ ውግዘቱ ዝርዝር ሁኔታዎች ይዘን እንቀርባለን ብለን በገባነው ቃል መሠረት ቀጣዩን ክፍል እነሆ፡፡
       እንግዲህ አባታችን አለቃ አያሌው ግዝቱን ካስተላለፉም በኋላ ዝም ብለው አልተቀመጡም፡፡ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ከዚህ መከረኛ ዓለም እስከተለዩበት እስከ ነሐሴ 14 ቀን 1999 ዓ.ም ድረስ፤በመኖሪያ ቤታቸው የቁም እስር ላይ ሆነው በየጊዜው የሚፈጠሩትን ስህተቶች በመቃወም፤ ከተለያዩ አቅጣጫ እቤታቸው ድረስ የሚሄዱትን ምእመናን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ በማስተማር፣ ከተለያዩ የግል ጋዜጠኞችና እንደ አሜሪካና ጀርመን በመሳሰሉ ሬዲዮ ጣቢያዎች የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመመለስና እንደሁም ከአራት በላይ መጻሕፍት በማዘጋጀት ሃይማኖታቸውን ጠብቀው ሩጫቸውን ጨርሰዋል፡፡
የተከበራችሁ የተዋሕዶ ልጆች፤
ከዚህ በመቀጠል አለቃ አያሌው ባስተላለፉት የግዝት ቃል ውሰጥ፤ ግዝት ለማስተላለፍ የተገደዱበትን ምክንያትና የችግሮቹን  እውነትነት የሚያረጋግጡልንን ጥቂት ማስረጃዎች እንመለከታለን፡፡

Saturday, August 18, 2018

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሃያ ስምንት

ከክፍል ሃያ ሰባት የቀጠለ
የዶግማና የቀኖና ጥሰት በኢ/ኦ/ ተ/ ቤተ ክርስቲያን፤ ክፍል አራት
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?
ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
ባለፉት ሦስት ተከታታይ ክፍሎች (ከ25-27) በስምምነቱ መግለጫ በተራ ቁ.2 "ስለ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት" በሚለው ርዕስ ውስጥ የተወሰኑ ሃሳቦችን ተመልክተናል፡፡በዚህ ክፍል ደግሞ ፤ቃለ ውግዘትን በተመለከተ እንቀጥላለን፡፡
መልካም ንባብ!

Wednesday, August 15, 2018

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሃያ ሰባት

ከክፍል ሃያ ስድስት የቀጠለ
የዶግማና የቀኖና ጥሰት በኢ/ኦ/ ተ/ ቤተ ክርስቲያን፤ ክፍል ሦስት
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?
ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
ሀ/ "የቀኖና ጥሰት" የቀጠለ
       ባለፉት ሁለት ክፍሎች በስፋት እንደተመለከትነው፤በተደጋጋሚ "የቀኖና ጥሰት" እየተባለ የሚነገረው "ፓትርያርክ በሕይወት እያለ ሌላ ፓትርያርክ አይሾምም" በሚለው ዙሪያ ይሁን እንጂ፤ (እሱም ተወራለት እንጂ መፍትሔ አላገኘም) የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን መሠረተ እምነቷንና ሥርዓቷን ትውፊቷን ሳይቀር የሚሸረሽሩ ፈርጀ ብዙ ችግሮች፤ዓይነታቸውና ብዛታቸው  ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ከላይ የተመለከትነው የአባቶቻችን መግለጫ፤ "…..ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ተላልፈው ለሞት ከተሰጡበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን…" በማለት እውነታውን ፍንትው አድርገው አሳይተውናል፡፡እንደሚታወቀው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ 2ኛው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ እንደሆኑ፤ይህንን የፓትርያርክነት ሹመት ያገኙት በአጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት እንደሆነ፤ ከዚያም ንጉሣዊውን ሥርዓተ መንግሥት በጉልበቱ አስወግዶ ሀገሪቱን በተቆጣጠረው ደርግ በተባለው ሃይማኖት የለሽ መንግሥት በግፍ ታፍነው እንደተገደሉ ታሪክ መዝግቦ አስቀምጦታል፡፡ቤተ ክርስቲያንም ምንም ዓይነት የፍትሕ ጥያቄ አለማቅረቧ ብቻ ሳይሆን ፤ቢያንስ አስከሬናቸው በተገቢው ሥፍራ በክብር እንዲያርፍ ሳታደርግ እንዲሁ "እንደ ንጉሡ አጎንብሱ" እንደሚባለው ሆኖ የደርግ መንግሥት እስከሚወድቅ ድረስ የከበረ አስከሬናቸው የነበረበት ሳይታወቅ ቆይቷል፡፡

Monday, August 13, 2018

“ ስለጽዮን ዝም አልልም ” ክፍል ሃያ ስድስት

ከክፍል ሃያ አምስት የቀጠለ
የዶግማና የቀኖና ጥሰት በኢ/ኦ/ ተ/ ቤተ ክርስቲያን፤ ክፍል ሁለት
የተወደዳችሁ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች! እንደምን ሰነበታችሁ?
ለዚች ዕለትና ሰዓት ያደረሰን የቅዱሳን አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ስሙ ይመስገን፡፡
       ባለፈው ጽሁፋችን በክፍል ሃያ አምስት ሁለቱን ሲኖዶሶች ወደ አንድነት ለማምጣት የተደረገውን የጋራ ስምምነት መግለጫ አስነብበናችሁ፤ቀጣዩን ክፍል በይደር አቆይተነው እንደነበር ይታወሳል፡፡በገባነው ቃል መሠረት እነሆ ዛሬ ሁለተኛውን ክፍል ይዘን ቀርበናል፡፡
መልካም ንባብ!